Ethiopian Electric Utility Woldia District

Ethiopian Electric Utility Woldia District Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Electric Utility Woldia District, WOLDIA, Woldia.

Permanently closed.
29/11/2017

በአዲስ አበባ በተወሰኑ ሥፍራዎች ለጥገና ሥራ የሚቋረጥ የኤሌክትሪክ ሀይል አቅርቦት,,,,,,,,,,
• በአንበሳ ጋራጅ፣ በኢምፔሪያል ሆቴል፣ በገርጂ ኮንዶሚኒየም፣ በዲ.ኤች ገዳ ፋብሪካ፣ በኢትዮ ፕላስቲክ ፋብሪካ፣ በኤክስ ኤል ፕላስቲክ ፋብሪካ እና አካባቢዎቻቸው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን፣
• ቅዳሜ ህዳር 23 ቀን 2010 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት እስከ ቀኑ 6፡00 ሰዓት እና፣
• እሁድ ህዳር 24 ቀን 2010 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡00 ስዓት እስከ ቀኑ 6፡00 ስዓት ድርስ
ለከፍተኛ መስመር የጥገና ስራ ሲባል የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚቋረጥ መሆኑን አውቃችሁ ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ታደርጉ ዘንድ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

29/11/2017

....በተደጋጋሚ እየተስተዋለ የሚገኘዉ የሀይል መቆራረጥና መዋዠቅ መንስኤዎች ምንድን ናቸዉ?...................
አብዛኛዉ ደንበኞቻችን/ተገልጋዮቻችን በተለያዩ ጊዜ በኤሌክትሪክ ሀይል መቆራረጥና መዋዠቅ የተነሳ ተደጋጋሚ ቅሬታዎች ለተቋማችን ያቀርባሉ፡፡
እንደ እኛ ነባራዊ ሁኔታ የኤሌክትሪክ ሀይል የሚቆራረጥበት ምክንያቶች……
• አብዛኛዉ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች(ፖሎች፣ ትራንስፎርመሮች፣ ኬብሎች፣ ወዘተ) ያረጁ ስለሆኑ የተገልጋዩን የሀይል ፍላጎት ለማርካት የሚያስችሉ ባለመሆናቸዉ፣
• የኤሌክትሪክ ሀይል ለማስተላለፍ በመሰረተ-ልማቶች ላይ የተገጠሙ አስፈላጊ ዕቃዎች በመስረቅ አላግባብ በሆነ መልኩ የማገናኘት ተግባር ማከናወን እና የኤሌክትሪክ ሀይል ስርቆት መኖሩ፡፡ ይህም ዋናዉ ሲስተማችን እንዲዛባ በማድረግ ሀይል በተደጋጋሚ እንዲቋረጥ ያደርጋል፡፡
• በተገልጋዩ ዘንድ ሀይል ያለአግባብ መጠቀም፣
• በተገልጋዩ ዘንድ ጥራታቸውን የጠበቁና ሃይል ቆጣቢ የአሌክትሪክ ዕቃዎችን ባለመጠቀምና ሥራዉንም በባለሞያ አለማሰራት፣
• በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ላይ በመኪናና በተፈጥሮ በሚደርሰዉ አደጋዎች፣
• በተለያዩ ጊዜ የጥገና ሥራ ሲከናወን ለጥንቃቄ ሲባል በዕቅድ ማቋረጥ፣
• እንዲሁም በሌሎች ምክንያቶች ይቋረጣል፡፡
ኤሌክትሪክ ጠቀሜታዉ እጅግ የላቀና በእያንዳንዳችን የዘመናዊ አኗኗር ዘይቤ ዉስጥ የደም ስር መሆኑ የማይካድ ነዉ፡፡ ሆኖም የኤሌክትሪክ ሀይል አቅርቦቱ ለተገልጋዩ በቋሚነት ካልቀረበ የሚያስከትለዉ ኢኮኖሚያዉ ጉዳትም ከፍተኛ ነዉ፡፡
ችግሩ እንደተቋም እኛም የምንገነዘበዉ ጉዳይ ሲሆን በዘላቂነት ለመቅረፍ እንዲቻል ዘርፈ-ብዙ ሥራዎችን እያከናወንን እንገኛለን፡፡
• ከእነዚህም በዚህ በጀት ዓመት ይጠናቀቃሉ ተብሎ የሚጠበቁትን አዲስ አበባን ጨምሮ በ8ት ትላልቅ ከተሞች እና በቀጣይነት በሌሎች 6ት ከተሞች የሚከናወኑት የኤሌክትሪክ ሀይል የማሰራጫ መስመሮችን የመልሶ ግንባት ፕሮጀክቶች አንደኛዉ ነዉ፡፡
• አገልግሎት አሰጣጣችንም ዘመናዊ ለማድረግ ኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒንግ የተሰኘ ሶፍትዌር ለመተግበር የመጨረሻዉ ምዕራፍ ላይ እንገኛለን፡፡
ነገር ግን ችግሮቹን በዘላቂት ለመፍታት በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ላይ የሚደረሰዉን ስርቆትና ጉዳት ከመከላከል አኳያ ህብረተሰቡም የበኩሉን ድርሻ መወጣት ይኖርበታል፡፡
ምንጭ:-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ኮሙኒኬሽን ዳሬክቶሬት

28/11/2017

ፕሮጀክቱ የማይነቃነቅ ደፋር ትውልድ ከመፍጠሩም በላይ ከቴክኖሎጂ ጥገኝነት ለማውጣት ያስቻለ መሆኑን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ስመኘው ተናገሩ፡፡
በውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን ሁሉ አንድ ያደረገው ፕሮጀክታችን ዋናው ግድብ ከሚያስፈልገው 10ነጥብ1 ሚሊዮን ኪዩቪክ ሜትር የአርማታ ሙሊት/RCC/ 7ነጥብ7 ሚሊዮን ኪዩቪክ ሜትር መሞላቱንም ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በህዳሴ ግድቡ ግንባታ ላይ የአርማታ ሙሊት በቀን፣በሳምት፣በወራትና ብሎም በአምት በዓለም ላይ እተሰሩ ካሉት ታላቅ ግንባታዎች ጋር ሲነፃፀር ቀዳሚነትን ይዟል፡፡ ይህንን አፈፃፀም መነሻ በማድረግ በቀጣዩ አመት ህዳር ሳይታጠን ምን ደረጃ ላይ ሊደርስ እንደሚችል መገመት አያዳግትም፡፡ ግድቡ በአለም ታላላቅ ከሚባሉ ግድቦች መካከል አንዱና ከአለም 7ኛ ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃ ላይ የሚፈረጅ ነው፡፡
ገናና ታሪክ የነበራትን ሀገራችንን ገናናነቷን እንደገና በማንሰራራት ማሳየት የሚችል ሃውልት ነው፡፡
ግድቡ የበለጸገችና መካከለኛ ገቢ ያላት ሃገር ለመፍጠር ታላቅ አቅም ስላለው ታላቁ የህዳሴ ግድብን ሁሉም አካላት የሙጥኝ ብሎ በጽናትና በአንድነት መጨረስ ይጠበቅበታል እንደ ኢንኢነሩ ሀሳብ።
እንደ ኢንጂነሩ ገለፃ ከግድቡ በስተጀርባ የሚገኙ 6 የሃይል ቤቶች 5 ተርቫኖችን በመምታት እያንዳንዳቸው 375 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል ለማመንጨት የሚያስችል ውሃ የሚንደረደርባቸው 6 ቱቦዎችን ተሰርተዋል፡፡
የግድቡ አንድ አካል የሆነው ሳድል ዳም 5 ነጥብ ሁለት ኪሎ ሜትር ርዝመትና 50 ሜትር ቁመት ያለው ሲሆን አጠቃላይ ስራዎች በመጠናቀቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ የዋናው ግድብ የቀኝና የግራ ጫፍ የ145 ሜትር የመጨረሻው ከፍታ ላይ የደረሰ ሲሆን ማዕከላዊ ክፍሉን የማገጣጠም ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተመላክቷል፡፡
ኪዚህም ሌላ የግድቡ የኢንጂነሪንግ፣ የመልሶ ማቋቋም፣ የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ሃይል ማስተላለፊያ መስመርዝርጋታ፣ የምንጣሮና የመሳሰሉትን ስራዎች ፅናትን የሚጠይቁ ተግበራትን አልፎ አሁን ካለበት ደረጃ መድረሱ አስደሳች ነው ብለዋል እንጂነር ስመኘው፡፡
ኢንጂነር ሰመኘው አክለውም ግድቡ የታችኛው ተፋሰስ አገራት ጥቅም ያማከለ ሲሆን ከሀገራቱ ጋር ያለውን መልካም ግንኙነት በመንገድ፣ በባቡር፣ በኤሌክትሪክ አቅርቦት ለመስተሳሰር መልካም እድል ይፈጥራል፡፡ የኤሌክትሪክ ሃይል ሲተርፈንና በማንጠቀምበት ጊዜ ለሃገራት የማካፈል ስራ ይሰራል።
ከሁሉም በላይ የቀጠናውን ሰላም በመጠበቅ የተፋሰስ አገራቱን እድገት በማፋጠን አገራዊ ፋይዳው ጉልህ ነው፣ የሀገራቱን በማህበራዊ፣ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር መጠነ ሰፊ ያደርገዋል።
መጠነ ሰፊ ትስስር ሲኖር እድገታችን ቀጣይነት ያለው መሆኑና ኢኮኖሚያችን የእያንዳንዱ ዜጋ የነፍስ ወከፍ ገቢ ከፍ እንደሚል እሙን ነው። እኛ ኢትዮጵያዊያን መስራት ስለምንችል፣ የተፈጥሮ ሃብቶቻችን ብዙ ስለሆኑ፣ ህዝቡ ትልቅ ራዕይ ያለን መሆንን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት አረጋግጧል፡፡ ስለሆነም የተለያዩ አገራት የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ የመለወጥ ትኩረት ያለው መሆኑን በማመነቻው በራካታ አገራት የፕሮጀክቱን ፍፃሜ በጉጉት በመጠባበቅ ላይ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ ታላቅ ፕሮጀከት የአገሪቱን እድገት ለማረጋገጥ ትክክለኛው መነሻ ከመሆኑም በላይ ሀገርን የሚያማክሩና በሃገር ጉዳይ ላይ መደራደር የሚችሉ ምሁሮችን ለመፍጠር ያስቻለ ነው፡፡
ለልማታችን ለእድገታችን ቁልፍ መሳሪያ የሁነው ታላቁ ህዳሴ ግድብ ትውልድን እያነፀ ያለ ለወደፊት የሚይነቃነቅ በስራ የሚያምን፣ በሃገሩ ልበ ሙሉ የሆነ ወጣትን ትውልድን ማነፅ እንደመሳሪያ ሆኗል። “ባይተዋር የነበርንበትን አለም አቀፍ ስምምነቶችንም የገረሰሰ ነው።”
የዘመኑ ታላቁ ስጦታችን “ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ “ሲጠናቀቅ የእያንዳንዱን ዜጋ የነፍስ ወከፍ ገቢ ከፍ በማድረግ መካከለኛ ገቢ ያላትን ሃገር ለማምጣትና የበለጸገችና የተሻለ ኑሮ የሚኖር ትውልድ የሚኖርባት ሃገር ትሆናለች፡፡
ኢንጂነር ስመኘው እንዳሉት እኛ ኢትዮጵያ ተቀራርበን፣ ተደማምጠንና ተደጋግፈን መስራት በመቻላችን ልዩነት ፈጥረናል፣ ከሁሉ በላይ ደግሞ ፕሮጀክቱ ከድህነት ብቻ ሳይሆን ከቴክኖሎጂ ጥገኝነት ለመላቀቅ አስችሎናል፡፡
እንደጀመርነው እንጨርሰዋለን እስክንጨርስ ድረስ የሚሰጠውን ጥቅም በማሰብ ያለንን አሟጠን እንጠቀማለን። የኢትዮጵያ መንግስትም ልማትን በማልማት ህብረተሰቦቹን ወደ ተሻለ የኑሮ ደረጃ ለማምጣት እየተጋ እንደሚገኝ በተግባር ያሳየ ፕሮጀክት ነው።
በግድቡ ዙሪያ እስካሁን ለተመዘገበው ስኬት የሚዲያው ተከታታይ የዘገባ ሽፋን በመስጠትና የህብረተሰብ የግንዛቤ ደረጃ በማሳደግ አቅም ፈጥሯል። ሚዲያው በአጠቃላይ ለሀገራችን እድገትና ገጽታ ግንባታ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ሲሆን ከዚህ በኋላም የተለመደውን ተግባር አጠናክሮ እንዲቀጥል ሲሉ አሳስበዋል፡፡
የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ህዳር 18/2010

27/11/2017

ብሄራዊ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መርሃግብር ይፋ ሆነ
“ብርሃን ለሁሉ” የተባለ ብሄራዊ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መርሃግብር በቀጣይ 7 ዓመት ውስጥ በመለው ኢትዮጵያ ሊተገበር ነው።
መርሃ ግብሩ በዛሬው እለት ይፋ የተደረገ ሲሆን፥ በሀይል አቅርቦት እጥረት ምክንያት የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ያልሆኑ የገጠራማ አካባቢዎችን ተደራሽ ያደርጋል ተብሎ ታምኖበታል።

ብሄራዊ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መርሃግብሩ ከዓለም ባንክ በተገኘ 375 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑም ተገልጿል።

በተጨማሪም መንግስት በየዓመቱ ለኤሌክትሪክ ሀይል ከሚበጅተው ገንዘብም ውስጥም የዚህ መርሃ ግብር ማስፈፀሚያ የሚካተት መሆኑም ታውቋል።

የብሄራዊ ኤሌክትሪክ አቅርቦት መርሃግብሩ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለመርያም ደሳለኝ ዛሬ በይፋ መጀመሩን አብስረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፥ መርሃ ግብሩ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ከማሳደግ ባሻገር ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ የሚኖረው ጠቀሜታ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

መርሃግብሩ በታሰበለት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ተግባራዊ እንዲሆን የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ ርብርብ እንዲያደርጉ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ጥሪ አቅርበዋል።

የውሃ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በበኩላቸው፥ መርሃ ግብሩ ሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የኤሌክትሪክ አገልግሎትን እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ብለዋል።

በተለይም በገጠርማ የሀገሪቱ ክፍሎች የኤሌክትሪክ ሀይልን ለማዳረስ የሚያስችል መሆኑንም አስታውቀዋል።

እንዲሁም በከተሞች አካባቢ በብዛት የሚስተዋለውን የኤሌክትሪክ ሀይል መቆራረጥ ችግርን በዘላቂነት የሚፈታ መሆኑን ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ተናግረዋል።

ብርሃን ለሁሉ የተሰኘው ብሄራዊ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መርሃ ግብር ፍኖተ ካርታም በዛሬው እለት ይፋ ተደርጓል።

መርሃ ግብሩ ገጠራማ የሀገሪቱ ክፍሎች ከፀሃይ ሀይል፣ ከጂኦ ተርማል እና ከሌሎች የሀይል ምንጮች ኤሌክትሪን እንዲያገኙ የሚያስችል ነው።

እንዲሁም ኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮች በውስጣቸው እያለፉ መብራት ለሌላቸው የገጠር ቀበሌዎችም ከማስተላለፊያው ላይ በመጥለፍ ኤሌክትሪክ ሀይል እንዲያገኙ በመርሃ ግብሩ ከሚሰሩ ስራዎች ውስጥ ይገኛል።

በዛሬው እለት ይፋ የተደረገው መርሃግብር በቀጣይ 7 ዓመታት ውስጥ የሚተገበር ነው።
ምንጭ ፦ ፋና ብሮድካስት /ኤፍ. ቢ. ሲ./

27/11/2017

ብሄራዊ የኤሌክትሪክ የተቀናጀ ፍኖተ ካርታ ፕሮግራም.
የሀገሪቱን የሃይል ፍላጎት እና ፍሰት በማመጣጠን ህብረተሰቡንና ኢኮኖሚዉን ለመደገፍ ያለመ ብሄራዊ የኤሌክትሪክ የተቀናጀ ፍኖተ ካርታ ፕሮግራም ይፋ ሊሆን ነው፡፡
ምንጭ EBC

25/11/2017

ውድ የፔጃችን ተከታታዮች በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፌስቡክ ገፅ የተቋማችን መረጃ እንደገና በቋሚነት ማስተላለፍ ከተጀመረ ከ20 ቀናት በላይ አስቆጥሯል ።
መረጃዉ የሚጫነዉ በተቋማችን የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ሲሆን በዚህ ገፅ የሚጫነዉ ሁሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አቋም የሚያንፀባርቁ መሆኑን እንድትገነዘቡ በዚህ አጋጣሚ እንገልፃለን፡፡
• እስካሁን በማእከላችን ስም በመክፍት ዉስን መረጃዎችን ለማስተላለፍ ሞክረናል ለዚህም ባጭር ጊዜ በርካታ ተከታዮች አፍርተናል።
በመሆኑም ተዓማኒ የሆኑ ወቅታዊ የተቋማችን መረጃዎች /መልዕቶች/እንዲደርስወት ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት --Ethiopian Electric Utility የሚለውን ገፅ ይመልከቱ።

25/11/2017

የአዲስ ኃይል አቅርቦት ማመልከቻ ሲጠየቅ የሚከተሉት ሰነዶችም መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡

1. አንድ ፎቶ ከመታወቂያ ጋር
2. የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ፤የሽያጭ ውል ፤የውርስ ስርተፊኬት
3. የይዞታውን ባለቤትነት በተመለከተ ክርክር ሲኖር ከሚመለከተው ፍርድ ቤት ትዕዛዝ መያያዝ ይኖርበታል፡፡
4. ከአካባቢው ባለስልጣን ፍቃድ የጸደቀ፤ ተቃውሞ ያለመኖር ሰነድ ስርተፍኬት ፤አስፈላጊ ከሆነ የህግ ትዕዛዝ
5. የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ፤የህንጻ ካርታ
6. የመንግስት ቤት ከሆነ ከመንግስት የተሰጠ ደብዳቤ
7. በገጠር ቦታዎች ከመንግስት አካል የተሰጠ ባለቤት ስለመሆኑ የሚገልጽ ደብዳቤ (የይዞታ
ማረጋገጫ ካርታ አያስፈልገውም )
8. የከተማ ቦታዎች ካርታ ከሌላቸው ከክፍለ ከተማ(ወረዳ) የተሰጠ ደብዳቤ፤
9. የቢል ቦርድ ፤የማስታወቂያ አገልግሎት ከተጠየቀ ከክፍለ ከተማ አስተዳደር የፍቃድ ደብዳቤ
10. የሽርክና ድርጅት ከሆነ የሽርክና መቋቋሚያ ደብዳቤ
11. ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ከሆነ የምስረታ አንቀጽ ፤የምስረታ ሰርተፍኬት፤የዳይሬክተሮች ዝርዝር አድራሻ መቅረብ ይኖርበታል፤
12. ለ7.5 ኪ.ዋ እና ከዚያ በላይ የኃይል ጭነት (3 ፊዝ እና ከዚያ በላይ ) የስራ ማጠናቀቂያ ሪፖርት እና የምርመራ ሰርተፊኬት በቅጹ መሰረት ፍቃድ ባላቸው ኤሌክትሪካል ስራ ተቋራጮች ተሞልቶ መቅርብ ይኖርበታል፡፡

24/11/2017

Ethiopian Electric Utility -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
ለሚመለከታቸዉ እንዲዳረስ~like~share~ ያደረጉ ዘንድ በመልካም ትብብር እንጠይቃለን,,
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,በዕቅድ የሚቋረጥ የኤሌክትሪክ ሀይል አቅርቦት…………..
በሰመራ፣በዲቼቶ፣ በሎጊያ፣ በሚሌ፣ በዱብቲ፣ በአሳይታ፣ በሰርዶ እና አካባቢዎቻቸው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን፣
• እሁድ ህዳር 17 ቀን 2010 ዓ.ም. ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ፣
• ለከፍተኛ መስመር የጥገና ስራ ሲባል የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚቋረጥ መሆኑን አውቃችሁ ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ታደርጉ ዘንድ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

24/11/2017

Ethiopian Electric Utility -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በቅርቡ ተግባራዊ ሊያደርግ ስላሰበዉ አዲስ ተቋማዊ የአደረጃጀት ማሻሻያ በጥቂቱ……….......
• የተገልጋዩን ፍላጎት ለማርካት ክልላዊ መዋቅር መሰረት በማድረግ የሚሻሻል ነዉ፡፡
• አሁን በስራ ላይ ያለው አደረጃጀት ወጪ ቁጠባ ላይ ትኩረት ያደረገ፣ አብዛኛው የተቋሙ የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት በማዕከል የተደራጀ እንዲሆን በማድረጉ፣ አሁን ህብረተሰቡና ክልሎች የሚያነሱትን የግልፀኝነትና የተጠያቂነት እንዲሁም የፍትሀዊ ተጠቃሚነት ጥያቄ በበቂ ሁኔታ መመለስ አልቻለም፡፡
• ስለዚህም በአዲሱ ክልላዊ የአደረጃጀት ማሻሻያ የህብረተሰቡን ጥያቄ መመለስ የሚችሉ ህልውና ያላቸው ተቋማት በክልል ደረጃ ይደራጃሉ፡፡
ጠቀሜታዉስ?..........
1. የመልካም አስተዳደር ችግር ይቀርፋል፣
2. ግልፀኝነትነና ተጠያቂነትን ያጠናክራል፣
3. የተቋሙ ዕቅድ ከክልል ዕቅዶች ጋር የተናበበ እንዲሆን ያስችላል፣
4. የህዝብ ተጠቃሚነትና የበላይነትን ያረጋግጣል፡፡
 ማሻሻያዉ በሠራተኛው ላይ የሚፈጥረው የምደባ መፈናቀል አያስከትልም፤ ምደባ የሚካሄደውም በፍቃደኝነትና በውድድር ነዉ፡፡
አደረጃጀቱ ውጤታማ እንዲሆን ከሠራተኛውና ከባለድርሻ አካላት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከት ይጠበቃል፡፡
በዚህ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ወደፊት ይዘን እንመጣለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ምንጭ፣ ዜና ፈለገ-ብርሃን
ቅጽ1/ቁጥር1/መስከረም 2010 ዓ.ም

09/11/2017

ዘርፍ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የኃይል ማከፋፈያና ማስላተላለፊያ ጣቢያዎች በመገንባት ላይ ይገኛሉ ፡፡
በአማራ ክልል ለተለያዩ ከተሞች፣ የገጠር መንደሮችና ለኢንዱስትሪ ዞኖች አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በመገንባት ናቸው፡፡ ከነዚህም መካከል የደብረብርሃን አዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ፣ የጎንደር እና ወልዲያ ነባር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የማስፋፊያ ግንባታ ሥራዎች ተጠቃሾች ናቸው፡፡
በደብረ ብርሃን እየተገነባ ያለው አንድ አዲስ ባለ 230 ኪ.ቮ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ሥራው በፍጥነት በመከናወን ላይ ሲሆን አጠቃላይ አፈፃፀሙም 50 በመቶ ደርሷል፡፡
የፕሮጀክቱ ጠቅላላ ወጪ 15,340,907 ዶላር እና 63,720,384 ብር ነው፡፡ በሌላ በኩል በኮምቦልቻና ጎንደር ለሚገኙ ነባር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የአቅም ማሳደግና የማስፋፊያ ሥራዎች በመከናወን ላይ ሲሆን አጠቃላይ አፈፃፀማቸውም ከ50 በመቶ በላይ ሊደርስ ችሏል፡፡
ለፕሮጀክቶች የተመደበውን የገንዘብ መጠንም የጎንደር 8,777,937 ዶላር እና 19,212,192 ብር ሲሆን የኮምቦልቻ ደግሞ 3,378,426 ዶላር እና 6,889,911 ብር ነው፡፡ እንዲሁም በኮምቦልቻ 50 ኤም ቪ ኤ አቅም ያለው አዲስ ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በመገንባት ላይ ሲሆን አጠቃላይ አራት ሚሊዮን ዶላር በጀት ተይዞለታል፡፡
በተጨማሪም በደሴ፣ ኮምቦልቻ፣ ዳባት፣ ደብረማርቆስ እና ባህርዳር ለሚገኙ ነባር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የመልሶ ግንባታ፣ የቤይ ማስፋፊያ፣ የትራንስፎርመር አቅም ማሳደግና የስዊች ጊር ገጠማ ሥራዎች ተከናውኖላቸው በአሁኑ ሰዓት በሙሉ አቅማቸው አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡
በተጨማሪም ለኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚሆን የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በተለያዬ የቮልቴጅ መጠን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና የማከፋፈያ ጣቢያዎች በመገንባት ላይ ሲሆኑ ከፕሮጀክቶች መካከል የባህር ዳር-ወልዲያ- ኮምቦልቻ ባለ 400/230 ኪ.ቮ የኃይል ማስተላለፊያ እና የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ይገኝበታል፡፡
የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮቹ እስከ 1000 ሜጋ ዋት ድረስ ኃይል የመሸከም አቅም ያላቸው ሲሆን ግንባታው የዲዛይን፣ የፍብረካ፣ የፍተሻ እና የኮሚሽኒንግ ሥራዎችንም ይጨምራል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
የውጪ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
አቶ ምስክር ነጋሽ
ጥቅምት 2010 ዓ.ም

14/09/2017

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በክልል ደረጃ በድጋሚ ሊዋቀር ነው
ከቀድሞው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ተከፍሎ የወጣው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ የክልል መዋቅሮችን ተከትሎ በድጋሚ ሊዋቀር ነው፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከአራት ዓመት በፊት ሲቋቋም ማኔጅመንቱ ለህንድ ኩባንያ ተሰጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ ውጤታማ ተቋም መገንባት ሳይቻል ቀርቷል፡፡ በዚህም ምክንያት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋምን ቀድሞ ወደነበረበት ለመመለስና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽንን በድጋሚ ለመፍጠር ታቅዶ ነበር፡፡

ይሁን እንጂ የውኃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስትሩ ስለሺ በቀለ (ዶ/ር)፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጎሳዬ መንግሥቴ፣ ሁለቱ ተቋማት እንደተለያዩ መቆየትና ይልቁንም መጠናከር እንደሚገባቸው በመስማማት የትግበራ ሥራ መጀመራቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ሪፖርተር ያነጋገራቸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጎሳዬ እንደሚሉት፣ ኃይል የማከፋፈል ሥራው በአገር አቀፍ ደረጃ በዘጠኙም ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ራሱን እየቻለ እንዲቋቋም ይደረጋል፡፡
‹‹አሁን በተቋሙ ሥር 15 ዲስትሪክቶች ቢኖሩም ሰባት የሚሆኑት በአንድ ክልል ውስጥ ይገኛሉ፡፡ የትኛው ምን እንደሠራ ማወቅም ስለማይቻል ለቁጥጥርም አመቺ አይደለም፤›› ብለዋል፡፡
በመሆኑም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትን የጎንዮሽ አወቃቀር በመጠቀም በሁሉም ክልሎች ለመበተን መታቀዱን ተናግረዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ጥናቱ እየተሠራ መሆኑን ያስታወቁት አቶ ጎሳዬ፣ ተቋማቱ ለጊዜው ለማዕከል ተጠሪ እንደሚደረጉና ወደፊት ግን ተጠሪነታቸውን ለክልሎች እንደሚሆን አክለዋል፡፡
የተቋሙ ሠራተኞች ራሳቸውን እያደራጁ በየክልሉ ከሚቋቋሙ የኃይል አቅርቦትና ጥገና ተቋማት ጋር መሥራት የሚችሉበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችልም ገልጸዋል፡፡
በቅርቡ የአማራ ክልላዊ መንግሥት ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ጋር በተያያዘ በደል እየደረሰብኝ ነው በማለት ቅሬታውን ማሰማቱ ይታወሳል፡፡
ክልሉ ባቀረበው ቅሬታ በአማራ ክልል ያሉ የኃይል ማስተላለፊያዎችና ትራንስፎርመሮች በደርግ ዘመን የተገነቡና ያረጁ መሆናቸውን፣ በዚህም ምክንያት በየጊዜው ለብልሽት ይጋለጣሉ ብሏል፡፡ 197 ኩባንያዎች ቢቋቋሙም የኃይል አቅርቦት ማግኘት ባለመቻላቸው ወደ ሥራ አለመግባታቸውንም ክልሉ መግለጹ አይዘነጋም

14/09/2017

ትልቅ ሸግግር!
የዲስትሪቢውሽን ትራንስፎርመር መከታተያ መሳሪያ በሚባል የሚታወቀው ዲ.ቲ.ኤም.ኤስ (DTMS- Distribution Transformer Monitoring System) በ20 ትራንስፎርመር ላይ ተገጥሞ የሙከራው ስራ ውጤታማ ሆነ፡፡
የመከታተያውን መሳሪያ ጥቅሙንና ለዲስትሪቢውሽን ስራ የሚያግዝበትን አጠቃላይ ፋይዳውን እንዲያብራሩልን የትግበራውን ስራ የሚመሩትን የድርጅቱ አንጋፋ ቴክኒሻን አቶ ብሩ ፀጋዬን ጠይቀን እንደሚከተለው አብራርተውልናል::
የመሳሪያው አጠቃቀም በእያንዳዱ ትራንስፎርመር ላይ ተገጥሞ የዘጠኙን መረጃ በRF ( በሬዲዮ ፍሪኪዎንሲ) ሞገድ በመጠቀም ማስተር ለተባለው አስረኛው ትራንስፎርመር የተገጠመው ላይ መረጃዎችን ይልካሉ፡፡ ይሄው ማስተር የተባለው በየ15 ደቂቃ የእያንዳንዱን ትራንስፎርመር ያለበትን አጠቃለይ ሁኔታ በተከፈተለት የመረጃ መረብ መሰረት ወቅታዊ መረጃዎችን የሚልክ እንደሆነ የነገሩን ሲሆን በእጅ ስልካቸውም ላይ በተሰጣቸው የሚስጥር የይልፍ ቁጥር ከፍተው መረጃውን ሲያዩ እኛም ተመልክተናል፡፡
የዚህን መሳሪያ ጥቅም እኚሁ ቴክኒሻን በተደሰተ በሚመስል መልኩ ለማብራራት ሲጀምሩ ተቋሙ ድል አግኝቷል ነው ያሉት፡፡ ሲቀጥሉ የተለመደው ስራ የአንድን ትራንስፎርመር ችግር ለማግኘት ቦታው ድረስ ሄደን ተደጋጋሚ የመለካትና የመፈተሸ ስራ ሰርተን ነው ችግሩን የምንፈታው፡፡ ይሄ ችግር እስኪፈታ ድረስ የመብራት መቋረጥ፤ በምልልስ የሚወጡ የግበአት ብክነት እና ትራንስፎርመሩን ከማዳን አንፃር አስቸጋሪ ነበር ስራችን፡፡ የዚህ መሳሪያ መምጣት ግን ስራችንን የተሳለጠ ያደርገዋል ነው ያሉት፡፡
ይሄ መሳሪያ ቢሮ ተቀምጠን በኮምፒውተር ወይም በእጅ ስልካችን ላይ ሆነን በተሰጠን የይለፍ ቁጥር ተጠቅመን የእያንዳንዱን ትራንስፎርመር ችግር በየ15 ደቂቃ ማወቁ ለተቋማችን ከምንጊዜውም በላይ በዲስትሪቢውሽን ዘርፍ ላይ የተጣለብንን ሀላፊነት በብቃት እንድንወጣ ያስችላል ብለውናል፡፡በተጨማሪ እኚሁን ቴክኒሻን መብራት ከመቆራረጥ አንፃር የሚሰጠውን ጥቅም እንዲነግሩን ጠይቀን ሲመልሱ የሚሰጠን መረጃ ብዙ ዓይነት ሲሆን ለምሳሌ ፊውዝ ሲቃጠል መብራት መቋረጡን፤ ጭነት ሲበዛ እና ዘይት ሲሞቅ የመሳሰሉትን የሚሰጠንና እኛም የደረሰንን መረጃ ይዘን የኃይል ማመጣጠን፤ ዘይት የመቀየር እና ያልተለመደ ጭነት ካየን የምርመራ ስራችንን በአፋጣኝ ለመስራትና ትራንስፎርመሩን ከመቃጠል ማዳን በእጅጉ ይረዳናል በሚል ጠቅልለው ገለፀውልናል፡፡
የመብራት መቆራረጥ ምክንያቶች የበዙ እንደመሆናቸው መጠን ይሄ መሳሪያ በትራንስፎርመር ዙሪያ የተቋረጠበትን ምክንያት ለመጠቆም ቅርብ ሆኖ መገኘቱ ለተቋሙ እፎይታ ይሰጠዋል፡፡
ተቋሙ የጥገና ፍላጎትን ለማሟላት የሚሄድበት ሁኔታ አዎንታዊዎችን ፍላጎት በተገቢው አካሄድ እንዳይሄድ ተግዳሮት እንደሆነበት ይታወቃል፡፡ የጥገና ፍላጎት ማደግ እየሰራ ያለውን አዎንታዊ ስራዎቹን በህብረተሰቡ ዘንድ ቅቡልነት ማጣቱ አሳሳቢ ነው፡፡የተቋሙ የስራው ባህሪ ከመኖሪያ ቤት ጀምሮ እስከ ኢንዱስትሪ ድረስ እያደገ የሚመጣ ፍላጎት እንደመሆኑ አኳያ ለሚገጥሙት እጥረቶች በግንዛቤዎች ላይ በሰፊው መሰራት እንዳለበት ይጠቁማል፡፡
በእድገት ጉዞ ላይ ወይም በሸግግር አካሄድ እጥረቶች ተፈጥሯዊ በሚመስል መልኩ መኖራቸው በህብረተሰቡ ዘንድ ግንዛቤው መኖርና የእጥረቱን ኃላፊነትንም ጭምር በጋራ መውሰድ እንደሚገባ ግንዛቤዎች ላይ በሰፊው መሰራት እንዳልነው ይሆናል፡፡
በመጨረሻም ተቋሙ ለተለያዩ ዘርፎች ስራ የለውጥ አማራጮች ናቸው ብሎ ለይቶ የጀመራቸው ስራዎች ሁሉ በተገቢው መንገድ መጓዛቸው በርታ ሲያስብለው እኛም እንደ ቴክንሺያኑ ድል ለ EEU እንላለን፡፡

Address

WOLDIA
Woldia
66

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Electric Utility Woldia District posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian Electric Utility Woldia District:

Shortcuts

Share